የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) ጋር ባደረጉት ውይይት ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች:-

=> ከተማዋ የምታመነጨው የገቢ ሁኔታ እና የሚሰበሰበው ገቢ ተመጣጣኝ አይደለም፤

=> ከለውጡ ወዲህ የገቢ መጠኑ በ3 እጥፍ አድጓል፤ በዚህም በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 30 ቢሊዮን ብር 100 ቢሊዮን ብር መድረስ ችሏል፤

=> የግብር መረብ ውስጥ ያልገቡ እና ግብር የሚሰውሩ በርካታ የንግድ አንቀሳቃሾች በከተማዋ ይገኛሉ፤

=> የቤት ግብር የዓለም ከተሞች የሚሰበስቡት የግብር ዓይነት ነው፤

=> አሁን እየተሰበሰበ የሚገኘው የቤት ኪራይና የቤት ግብር ደንብ ከ45 ዓመት በፊት የነበረ ደንብ ነው

=> የክፍያ መጠኑ አሁን ላይ ያለውን የኢኮኖሚ ሁኔታ እና እንቅስቃሴን መሰረት ያደረገ ነው፤

=> የግብር መጠኑ ጥናት ተደርጎ የግብር ስሌት ምጣኔው ቀድሞ የነበረው ሳይነካ ፤ የገንዘብ መጠኑ ነው ማሻሻያ የተደረገበት፤

=> መኖሪያ ቤቶች የሚከፍሉት በስሌቱ ተሰርቶ የሚመጣውን 50 በመቶ ብቻ ሲሆን የንግድ ቤቶችና መስርያ ቤቶች ደግሞ 75 በመቶ ብቻ ነው፤

=> በአዲስ አበባ ያለቁና አገልግሎት እየሰጡ ካሉ 800 ሺህ የመኖርያ ቤቶችና የንግድ ቤቶች ውስጥ 182 ሺህ ቤቶች ብቻ ነበሩ በግብር ስርዓት ውስጥ የነበሩት፤

=> የቤት ግብር የሚሰበሰበው የማይከፍለው ከሚከፍለው የሚበልጥ በመሆኑ እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ህብረተሰብ ክፍሎች ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ለማድረግ ነው፤

=> ለህዝቡ በድጎማ የሚቀርቡ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ ፍትሃዊ የግብር ስርዓት ያስፈልጋል፤

=> የኑሮ ውድነት ጫና ያለበት ዝቅተኛ ገቢ ያለው የማህበረሰብ ክፍል ቢሆንም ግብር እየከፈለ ያለው ይሄው የማህበረሰብ ክፍል ነው፤

=> ከሚያዝያ ወር ጀምሮ 91 ሺህ ነዋሪዎች የከፈሉ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 62 በመቶ የሚሆነው የጋራ መኖርያ ቤት ነው፤

=> እስካሁን ከዚህ የግብር ዓይነት 600 ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል፤

=> አብዛኞቹ የመኖሪያ ቤቶች ግብራቸውን ከፍለዋል፤

=> የአገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ ተጨማሪ ሰራተኞች ተመድበው እየሰሩ ነው፤

=> በቀጣይ በቤት ግብር ውስጥ የማይካተቱ ዜጎችን በተመለከተ ጥናት እየተካሄደ ነው፤

=> የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር በየዓመቱ ከ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ለከተማዋ ነዋሪዎች ድጎማ ያደርጋል፤

=> በአዲስ አበባ እየተገነቡ ካሉ የህዝቡን ኑሮ ማቅለያ ምርት የሚይዙ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት ውስጥ 2ቱ የተጠናቀቁ ሲሆን ሁለቱ በቅርቡ ይጠናቀቃሉ፤

=> የቤት ግብር ተከራይ ላይ ኪራይ ለመጨመር ምክንያት የሚሆን ጉዳይ አይደለም፤

=> የቤት ኪራይ የሚጨምሩ አከራዮችን ለመቆጣጠር ለክፍለከተሞች እና ወረዳዎች መመርያ ተላልፏል፤

=> ኢ-ፍትሃዊነትን ለማስተካከል ማህበረሰቡ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በጋራ ሊሰራ ይገባዋል፤

=> ለነዋሪዎች የመኖርያ ቤት አማራጮችን ለማቅረብ ከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፤

Leave a Reply