የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኤች አይ ቪ ኤድስ በተመለከተ በማዕከል እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ለሚገኙ ሰራተኞች ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ለሁለት ቀናት ስልጠና በተደረገበት ወቅት እንደተገለፀው ሰራተኛው ራሱን ከበሽታው በመከላከል በቫይረሱ ሰላባና ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን መታደግ እንደሚገባ ተገልል፡፡
ስልጠናው በኤች አይ ቪ/ኤድስ የሞቱ አካላትና ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ህፃናትና ቤተሰቦቻቸውን ለማስታወስ አንዲሁም ህብረተሰቡ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ምርመራ በማድረግ እራሱንና ወገኑን ከ በሽታው መታደግ እንደላበት ለማሳሰብ ታቅዶ የተዘጋጀ ነው፡፡
ስለሆነም ሰራተኞች የበኩላቸውን ሚና በመወጣት በተለይ በቫይረሱ ስላባና ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን መታደግ እንዳለበቸውም በስልጠናው ወቅት ተጠቁሟል፡፡
![](http://aatb.gov.et/wp-content/uploads/2024/02/427791616_894560306007676_4150096545276095213_n.jpg)
![](http://aatb.gov.et/wp-content/uploads/2024/02/427786334_894560502674323_5600681825016042192_n.jpg)
![](http://aatb.gov.et/wp-content/uploads/2024/02/427756302_894560346007672_8164293425839126016_n.jpg)